Monday, August 22, 2011

ጾመ ፍልሰታ።


ነሐሴ ፩ ቀን ፳፻ ዓ∙ ም∙


እንኳን ለጾመ ፍልሰታ በሰላም አደረሰዎ። ጾመ ፍልሰታ እንደሚታወቀው በአገራችን ዐዋቂዎች ብቻ ሳይሆኑ ሕፃናት ሳይቀሩ የሚጾሙት ጾም ነው። ጾሙም ብዙ ጸጋና በረከት የሚያሰጥ ነው።
ይህ ጾም እንዴት እንደ ተጀመረ ታሪኩን የሚገልጸውን የድምፅ ፋይል ከድምፅ ማኅደር ማውረድ ይችላሉ። የድምፅ ፋይሉ የተቀረጸው በ፲፱፻፺፰ ዓ፤ ም፤ ሲሆን ያስተማሩትም አለቃ አያሌው ታምሩ ናቸው።
አባታችን ለጾመ ፍልሰታ ልዩ ፍቅር የነበራቸው ሲሆን በዚህ ጾም ጊዜ ከአባቶቻቸው እንደ ወረሱት በየዕለቱ ማለዳ ውዳሴ ማርያምንና ቅዳሴ ማርያምን በአንድምታ የመተርጐም ልምድ ነበራቸው። በየዕለቱ ማታ ማታም እንደ ዘወትር ሁሉ ውዳሴ ማርያምን በዜማ ያደርሱ ነበር። በዜማ ያደርሱት ከነበረው በ፲፱፻፺፬ ዓ፤ ም፤ የተቀረፀውን ከድምፅ ማኅደር ውስጥ ማውረድ ይችላሉ። እንዲሁም በ፲፱፻፺፰ ዓ፤ ም፤ ጾመ ፍልሰታ የተቀረጸውን የውዳሴ ማርያም የአንድምታ ትርጕም ከዚሁ ከድምፅ ማኅደር ውስጥ ማውረድ ይችላሉ።
አምላካችን ጾሙን የተባረከ ያድርግልን።

2 comments: